ሌሎች እንዲለወጡ እንደምንፈልገው እራሳችንን እንለውጥ

ዛሬ የብዙወቻችን ችግር ኢልም አይደለም ተግባሩ እንጂ። ብዙወቻችን አንብበናል ፣ ሰምተናል ፣ አውቀናልም። ነገርግን ከአስተማሪውም ሆነ ከተማሪው የተግባር ሰው ጠፍቷል። መካሪው እና ተመካሪው እኩል ሆኗል።

በእርግጠኝነትና በቆራጥ ውሳኔ መንቃት የምንፈልግ ሁሉ በዚህ የቁርአን አንቀፅ እንንቃ!

“እናንተ ያመናችሁ ሆይ የማትሰሩትን ነገር ለምን ትናገራላችሁ።”

{አል-ቁርአን 61:2}

በሱረቱል በቀራ አንቀፅ 44 ላይ እንዲህ ይላል:-

“እናንተ መጽሐፉን የምታነቡ ሆናችሁ ሰዎችን በበጎ ስራ ታዛላችሁን? ነፍሶቻችሁንም ትረሳላችሁን? የስራዎቻችሁን መጥፎነት አታውቁምን?”

{አል-ቁርአን 2:44}

አይሁዶች መጽሐፍ ተሰቷቸው ስላልሰሩበት በአህያ ተመሰሉ አሏህ በቁርአኑ በሱረቱል ጁምአ አንቀፅ 5 ላይ እንዲህ ይለላል:-

“የእነዚያ ተውራትን የተጫኑትና ከዚያም ያልተሸከሟት (ያልሰሩባት) ሰዎች ምሳሌ መጽሐፎችን እንደሚሸከም አህያ ቢጤ ነው። የእነዚያ በአሏህ አንቀጾች ያስተባበሉት ህዝቦች ምሳሌ ከፋ። አሏህም በዳዮችን ህዝቦች አይመራም።”

{አል-ቁርአን 62:5}
Share the Post:

Related Posts

መረጃ እና አስፈላጊነቱ

መረጃ ትርጉም ያለው መልዕክት ሆኖ ከአንድ ምንጭ ወደ ተጠቃሚ የሚተላለፍ ነው፡፡ ስለአንድ ነገር መግለፅ የሚያስችለን  ነው፡፡ ይህ መረጃ ከግለሰብ አስተሳሰብ

Read More
ተውባ
Ahmed Yesuf

ተውባ

ተውባ ማለት ሃጢያትን ወይም ወንጀልን ከሰራንና ከአሏህ(ሱ.ወ.ተ) ጋር ያለንን ትስስር አደጋ ላይ ከጣልን ብኻላ ወደ አሏህ በፀፀት መመለስ ማለት ነው።

Read More

Join Our Newsletter

Scroll to Top