ጊዜና ልጅነት

ቀን ቀንን ሲተካ ሲከንፍ እንደዋዛ፤
ሲመለሱ አይኖርም ያረገፉት ጤዛ፤

እንዲህ ነው ልጅነት በቀን የሚጨልም፤
ካለፈ በኋላ የማይኖሩት አለም፤

የማለዳ ፀሐይ አምሮባት የዋለች፤
ሰአቷን ጠብቃ ማታ ትጠልቃለች፤

ጊዜው እየሮጠ እድሜ እየከነፈ፤
ከቀን ጋር ተዋግቶ የለም ያሸነፈ፤

ልጅነት በጊዜ ጦር እየተመታ፤
የማለዳ ውበት አይገኝም ማታ፤

የሰው ልጅ ሁልጊዜ ልጅነት ቢመኝም፤
ልጅ እንጅ ልጅነት ዳግም አይገኝም፤

ምንጭ_______በአራጋው ሙሐመድ

Share the Post:

Related Posts

መረጃ እና አስፈላጊነቱ

መረጃ ትርጉም ያለው መልዕክት ሆኖ ከአንድ ምንጭ ወደ ተጠቃሚ የሚተላለፍ ነው፡፡ ስለአንድ ነገር መግለፅ የሚያስችለን  ነው፡፡ ይህ መረጃ ከግለሰብ አስተሳሰብ

Read More
ተውባ
Ahmed Yesuf

ተውባ

ተውባ ማለት ሃጢያትን ወይም ወንጀልን ከሰራንና ከአሏህ(ሱ.ወ.ተ) ጋር ያለንን ትስስር አደጋ ላይ ከጣልን ብኻላ ወደ አሏህ በፀፀት መመለስ ማለት ነው።

Read More

Join Our Newsletter

Scroll to Top