እማየ ውለታሽ ብዙ ነው

እማየ ውለታሽ ብዙ ነው

እናት አለም ክብሬ እማየ አንደቤቴ፤
የመኖሬ ዋስትና የዘጠኝ ወር ቤቴ፤
በደምሽ ታንፃ መልካሟ ህይወቴ፤

እኔ ስስቅ ስቀሽ ስከፋ ተከፍተሽ፤
ሲርበኝ ተርበሽ
ሲጠማኝ ተጠምተሽ፤

በመልካሙ ምኞት መልካሙን አስበሽ፤
የወደፊት ተስፋየን ህይወቴን አብርተሽ፤

ለፍተሽ ጥረሽ ግረሽ ደክመሽ አስተምረሽ፤
ስሳሳትም መክረሽ ሃሳቤን ቀይረሽ፤

ትክክለኛውን መንገድ መስመሩን አስይዘሽ፤
በርካታ ቢሆንም እማየ ውለታሽ፤
ውለታሽን ከፋይ ልሆን ቃል ስገባልሽ፤
የህይወቴ ብርሃን እማየ እንዳይከፋሽ፤

የትላንቱ ህፃን ዛሬ ሰው ሁኛለሁ፤
ክፉና በጎውን ማስታወስ ችያለሁ፤
እናት አለም ክብሬ ሁሌም እወድሻለሁ!!!

“ጌታችሁም ከእሱ በቀር ያለን ነገር እንዳታመልኩ እና ለቤተሰቦቻችሁ ቅን ትሆኑ ዘንድ ደነገገ። በአንተ ዘንድ ሆነው አንዳቸው ወይም ሁለታቸው የእርጅና እድሜ በደረሱ ጊዜ ኡፉ አትበላቸው፤ አትገላምጣቸውም። መልካምን ቃል ተናገራቸው። ለእነሱ የሽንፈትና የውርደት ክንፍህን በእዝነት ዝቅ አድርግላቸው። እናም «ጌታዬ ሆይ! በሕፃንነቴ (በርኅራኄ) እንዳሳደጉኝ ሁሉ ምህረትህን ስጣቸው» በል።”

{አል-ቁርአን 17:23-34}
Share the Post:

Related Posts

መረጃ እና አስፈላጊነቱ

መረጃ ትርጉም ያለው መልዕክት ሆኖ ከአንድ ምንጭ ወደ ተጠቃሚ የሚተላለፍ ነው፡፡ ስለአንድ ነገር መግለፅ የሚያስችለን  ነው፡፡ ይህ መረጃ ከግለሰብ አስተሳሰብ

Read More
ተውባ
Ahmed Yesuf

ተውባ

ተውባ ማለት ሃጢያትን ወይም ወንጀልን ከሰራንና ከአሏህ(ሱ.ወ.ተ) ጋር ያለንን ትስስር አደጋ ላይ ከጣልን ብኻላ ወደ አሏህ በፀፀት መመለስ ማለት ነው።

Read More

Join Our Newsletter

Scroll to Top