ቢድአ (ፈጠራ በኢስላም)
ቢድአ ማለት ከቁርአን ፣ ከሐዲስ ፣ ከሸሪአ መሰረት የሌለው እና በረሱል (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) እና በነዛ ብርቅየ ሶሃቦች ዘመን ያልነበረ ወይም ያላደረጉት የኢባዳ ተብየ አይነቶችን ሁሉ የሚያጠቃልል እና ከራሳችን ፍልስፍናና ስሜት በመነሳት ያልነበሩ ነገሮችን በዲነል ኢስላም ላይ መጨመር ነው።
ቢድአ ማለት ከቁርአን ፣ ከሐዲስ ፣ ከሸሪአ መሰረት የሌለው እና በረሱል (ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም) እና በነዛ ብርቅየ ሶሃቦች ዘመን ያልነበረ ወይም ያላደረጉት የኢባዳ ተብየ አይነቶችን ሁሉ የሚያጠቃልል እና ከራሳችን ፍልስፍናና ስሜት በመነሳት ያልነበሩ ነገሮችን በዲነል ኢስላም ላይ መጨመር ነው።
ሸይጧን ጭስ አልባ ከሆነ እሳት የተፈጠረ ሲሆን መላኢካ ባይሆንም ለአሏህ በነበረው ታዛዥነት ግን በጀነት ከነሱ መካከል ነበር። አሏህ(ሱ.ወ.ተ) አደም(ዐ.ሰ) በፈጠረ ጊዜ በጀነት ያሉ ሁሉ ከአደም(ዐ.ሰ) ፊት ለፊት ይሰግዱ ዘንድ አዘዛቸው። ነገር ግን ሸይጧን በእብሪተኝነት እና በኩራት
ቁርአን ግልፅ የሆነ ልንስራራበት እና ልናስተነትንበት የሚገባ ሲሆን ለሰው ልጆች በረካ የሆነ መለኮታዊ መጽሐፍ ነው። አሏህ(ሱ.ወ.ተ) ቁርአንን ታዓምር ፣ በረካ ፣ አዳኝ ፣ አስታዋሽ በሚሉ ባህሪያት ጠርቶታል
ልኡል ሃያል ስለሆነው አሏህ ያለ እውቀት ስለ እሱ መናገር የከፋ የአሏህን ቅጣት የሚያመጣ ሲሆን ከወንጀሎችም ሁሉ የከፋ ወንጀል ነው። በዚህም ምክኒያት በማንኛውም ሁኔታ ላይ ሁነን ቢሆን እንኳ ያለ እውቀት ስለ አሏህ መናገር አይኖርብንም። አሏሁ አዘወጀል በሱረቱል አዕራፍ ከሌሎች ከባባድ ወንጀሎች ጋር እያወዳደረ የወንጀሉን ከባድነት ገልፆልናል
ኢባዳ የሚለው ቃል ሸሪአዊ ፍቹ አሏህ የሚወደው ማንኛውም በግልፅም ይሁን በድብቅ የሚሰራን፤ በንግግር እና በተግባር የሚገልፅን ስራ ሁሉ የሚያጠቃል ቃል ነው። ሸኹል ኢስላም ኢብንተይሚያ ኢባዳ ማለት አሏህ በመልዕክተኛው ምላስ ያዘዘውን ነገር በመከተል አሏህን መታዘዝ ነው ብለዋል።
ኒቃብና ቡርቃ ኢስላማዊ መሠረት ያላቸው ስለመሆኑ ምንም የሚያማያጠራጥር እና ጥያቄ የማያስነሳ ጉዳይ ነው። ቀደምት ሙስሊም ሴቶችም እራሳቸውን በነዚህ አልባሳት ይሸፋፍኑ እንደነበር ብዙ የታሪክ መዛግብት ያመላክታሉ። ሆኖምግን ኒቃብና ቡርቃ ግዴታ ናቸው ወይንስ በፍላጐት የሚደረጉ ናቸው በሚለው ዙርያ
ሂጃብ የፊጥራ(የተፈጥሮ ባህሪ ) ክፍል ነው።ይህን በጥልቅ ለመረዳት ተፈኩር(ማስተንተን) ጠቀሚ ነው። በዙሪያሽ ያሉ ነገሮችን ተመልከች ሁሉም ሽፋን አላቸው። ለምሳሌ መሬት በከባቢ አየር የተሸፈነች ናት፤ የውስጥ የአካል ክፍሎች ፣ ሴሎች ፣ ማእድናት ፣ ፍራፍሬ ወዘተ የራሳቸው የሆነ መሸፈኛ አላቸው፤ ቆዳሽ ብርሃን አስተላላፊ ቢሆን ኖሮ
ማንኛውም ሰው ህይወቱን በተለያየ መንገድ ያሳልፋል። ነገር ግን ወሳኙ ጥያቄ የህይወቱን ሃቅ የሞላ ወይም የፈፀመ ማነው? የሚለው ነው። እንስሳቶች የህይወታቸውን እያንዳንዷን ጊዜ እንዲሁ ያሳልፋሉ። ነገርግን ጊዜውን በጥበብ የተሰጠው የሰው ልጅ የተለያዩ ነገሮችን በመፈፀም ያሳልፋል።
ጀነት ሃያሉ አሏህ ለደጋግ ባሮቹ ያዘጋጀው ዘላለማዊ የደስታ ቤት ነው፡፡ ይህ ዘላለማዊ ደስታ አይን አይቶት ፣ ጆሮ ሰምቶት የማያውቅ ነው፡፡ ነብዩ(ﷺ) ስለ ጀነት ሲናገሩ ‹‹አይን አይቶት ፣ ጆሮ ሰምቶት ፣ የሰው ልጅ ልብ አስቦት የማያውቅ ነገር አሏህ ለባሮቼ አዘጋጅቻለሁ አለ›› ብለዋል፡፡ ይህን ሐዲስ ያስተላለፉት አቡ ኹረይራ የሚከተለውን የቁርአን አያ አያይዘው ጠቀሱ ‹‹ይሰሩት ለነበረው ምንዳ የአይን